አትሌቲክስ

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ በበርሚንግሃም የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ሩጫ አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 18፣ 2015 አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ በእንግሊዝ በርሚንግሃም በተካሄደው የዓለም አትሌቲክስ የሴቶች 3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ሩጫ ድል ቀንቷታል፡፡

አትሌቷ ርቀቱን በ8 ደቂቃ 16 ሰከንድ 69 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ነው ያሸነፈቸው፡፡

በዚህም አትሌት ጉዳፍ አዲስ ክብረ ወሰን ለማስመዝገብ 9 ሰከንድ የቀራት መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ሩጫ ክብረወሰን በሌላኛዋ ኢትዮጵያዊ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ የተያዘ መሆኑን ከወርልድ አትሌቲክስ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ተመሳሳይ ልጥፎች

በቶኪዮ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል

admin

አስተያየት ይስጡ