
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፓኪስታን ካራቺ ከተማ በሳምንት አራት ቀን የሚያደርገውን በረራ ዛሬ ማምሻውን ጀመረ
አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ(ኤ ኤም ኤን) ሚያዝያ 30/2015 ዓ.ም
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ20 አመታት በኋላ ዳግም ወደ ፓኪስታኗ የንግድ ከተማ ካራቺ በሳምንት አራት ቀን የሚያደርገውን በረራ ዛሬ ማምሻውን መጀመሩን ከአየር መንገዱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
አየር መንገዱ ወደ ካራቺ ከተማ የጀመረው በረራ በሳምንት አራት ጊዜ የሚደርግ ሲሆን ይህም አየር መንገዱ ወደ እስያ የሚያደርገውን የበረራ መዳረሻ ወደ 37 ከፍ ያደርገዋል።