
አክሞን ሊንክ ኮሌጅ በተለያየ የትምህርት ደርጃ ያሰለጠናቸውን 5 መቶ 96 ተማሪዎችን አስመረቀ
አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኤ ኤም ኤን) ሀምሌ 23/2015 ዓ.ም
በምርምር በትምህርት እንዲሁም በማህበረሰብ አገልግሎት እየሰራ የሚገኘው ይህ ኮሌጅ በዲፕሎም 1 መቶ 80 በድግሪ 48 እንዲሁም በሁለተኛ ድግራ 3 መቶ 64 ተማሪዎችን በማስመረቅ ላይ መሆኑን ያበስሩት
የአክሞን ሊንክ ኮሌጅ ፕሬዝዳንት ረዳት ፕሮፌሰር ተሻለ ጌቱ ኮሌጁ በትምህርት ልህቀት ብሎም በማህበረስብ አቀፍ ተግባራት እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
በትምህርት የዳበረ ትውልድ ማፍራት የችግር መፍቻ ነው ያሉት ደግሞ የመስኖና ቆላማ አከባቢዎች ሚንስቴር ዴኤታ ዶክተር ብርሃኑ ሌጂሶ ናቸው።
ተመራቂ ተማሪዎች ለዚህ ትልቅ ድርሻ ይኖራቸዋል ብለዋል። ማህበረስቡን ዝቅ ብሎ ማገልገል ይገባልም ሲሉ መክረዋል።