
አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ( ኤ ኤም ኤን) ሀምሌ 23 ቀን 2015 ዓ.ም
ሩሲያ የሰላም አማራጮችን እንደማትቃወም የሩሲያው ፕሬዝደንት ቪላድሚር ፑቲን አስታወቁ፡፡
የአፍሪካ አገራትና ቻይና ያቀረቡት የሰላም ሀሳብ ለሩሲያ ና ዩክሬን ጦርነት መርገብ እንደ መፍትሄ ሊወሰድ ይችላል ብለዋል፡፡
ይሁን እና የዩክሬን ወታደሮች መከላከል እስካላቆሙ ድረስ የተኩስ አቁም ስምምነት አይታሰብም ብለዋል፡፡
ፕሬዝዳንት ፑቲን ይህን ንግግር ካደረጉ ከሰአታት በኋላ የዩክሬን ድሮኖች በሞስኮ ባደረሱት ጥቃት በአንድ መስሪያቤት ሁለት ቢሮዎች ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን ሞስኮ ገልጻለች፡፡በጥቃቱ አንድ ሰው መጎዳቱ ተገልጿል፡፡
ዩክሬን በጉዳዩ ላይ ያለችው ነገር የለም መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡