ህብረተሰቡን ያሳተፉ ስራዎች በመሰራታቸዉ በከተማዋ ሰላምና ጸጥታ የተረጋገጠ ሆኗል ፡- የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ

You are currently viewing ህብረተሰቡን ያሳተፉ ስራዎች በመሰራታቸዉ በከተማዋ ሰላምና ጸጥታ የተረጋገጠ ሆኗል ፡- የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ

AMN – ጥቅምት 14/ 2017 ዓ.ም

ህብረተሰቡን ያሳተፉ ስራዎች በመሰራታቸዉ ከተማዋ ሰላምና ጸጥታዋ የተረጋገጠ እና ለኑሮ ምቹ እንድትሆን ማስቻሉን የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ ።

ቢሮዉ የበጀት አመቱን ሩብ አመት አፈጻጸም ከህዝብ አደረጃጀት ዘርፍ ጋር ገምግሟል ።

የቢሮዉ ምክትል ሃላፊ አቶ ሚደቅሳ ከበደ ቢሮው 11 ሺህ ወጣት የሰላም ሰራዊት አሰልጥኖ ከነባር የሰላም ሰራዊት ጋር እንዲቀላቀሉ ማድረጉን ፣ በከተማዋ የጫኝ እና አዉራጆችን አሰልጥኖ ወደ ስራ ማስገባቱን ተናግረዋል ።

ከአንድ ሚሊየን በላይ የሚሆኑ የህብረሰብ ክፍሎችን በሰላም ዙሪያ ማወያየቱ በሩብ አመቱ ከነበሩ አንኳር ተግባራት መካከል መሆናቸዉን አንስተዋል ።

በተለይ ህብረተሰቡን ያማከሉ በርካታ ተግባራት መተግበራቸዉ የአዲስ አበባን ሰላም ማጠናከር ተችሏልም ብለዋል ።

የበጀት አመቱ ሩብ አመት በከተማዋ በርካታ የአደባባይ በአላትንና አለም አቀፋዊ ጉባኤዎችን ያለምንም የጸጥታ ችግር ያከናወነችበት እንደነበርም አንስተዋል ምክትል ቢሮ ሃላፊዉ ።

ለዚህ ስኬት የህብረተሰብ አደረጃጀት የአንበሳዉን ድርሻ ተወጥቷልም ብለዋል ።

በአለማየሁ አዲሴ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review