AMN-ጥር 4/2017 ዓ.ም
ለሀገራቸው እና ህዝባቸው በትልቅ ብቃት ፣በታማኝነት፣ በሀቀኝነት ፣ በላቀ ስብዕና ያገለገሉ የሀገር ባለውለታ የሆኑትን የአቶ ቡልቻ ደመቅሳን የአስክሬን ሽኝት ስነ-ስርዓት መፈጸማቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡
ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ ፈጣሪ ለቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መፅናናትን እንዲሰጥ ተመኝተዋል፡፡
“ፈጣሪ ነፍሳቸውን በአጸደ ገነት ያኑርልን” ሲሉም ገልጸዋል፡፡