AMN – የካቲት 9/2017 ዓ.ም
የሴራሊዮን ቀዳማዊት እመቤት ፋጢማ ማዳ ባዮ (ዶ/ር) የአፍሪካ ቀዳማዊት እመቤቶች ድርጅት ሊቀ መንበር ሆነው ተመርጠዋል።
የአንጎላዋ ቀዳማዊት እመቤት አና ዲአስ ላውሬንኮ ደግሞ ምክትል ሊቀ መንበር ሆነው ተመርጠዋል።
ቀደማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው አዲስ ለተመረጡት ቀዳማዊት እመቤቶች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ማስተላለፋቸውን ከጽሕፈት ቤታቸው የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡