በሀሰተኛ መታወቂያ ፣ የጋብቻ ሰርተፊኬት እና የልጃቸውን የልደት ሰርተፊኬት ለማግኘት የሞከሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

You are currently viewing በሀሰተኛ መታወቂያ ፣ የጋብቻ ሰርተፊኬት እና የልጃቸውን የልደት ሰርተፊኬት ለማግኘት የሞከሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

AMN- ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም

በሀሰተኛ መታወቂያ ፣ የጋብቻ ሰርተፊኬት እና የልጃቸውን የልደት ሰርተፊኬት ለማግኘት የሞከሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የመኖሪያ አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ ፡፡

በየካ ወረዳ 7 የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ፅ/ቤት በቀን 29/1/2017 ዓ.ም በሀሰተኛ መታወቂያ የጋብቻ ሰርትፍኬት እና የልጃቸው ልደት ለማግኘት የሞከሩ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጎ ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሚገኝ ነው ኤጀንሲው በመረጃው ያስታወቀው፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review