በሚሌ ከተማ ከቦቴ ነዳጅ በመቀሸብ ሲሸጡ የተደረሰባቸው በቁጥጥር ስር ዋሉ

You are currently viewing በሚሌ ከተማ ከቦቴ ነዳጅ በመቀሸብ ሲሸጡ የተደረሰባቸው በቁጥጥር ስር ዋሉ

AMN – ሚያዝያ 6/2017

በአፋር ክልል ሚሌ ከተማ ከቦቴ ነዳጅ በመቀሸብ ሲሸጥ እጅ ከፍንጅ የተደረሰበት ሾፌርና ተቀባይ በቁጥጥር ስር ዋሉ።

የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አህመድ አብዱልቃድር ከጅቡቲ ነዳጅ ጭኖ ወደ አዲስ አበባ በመንቀሳቀስ ላይ የነበረ አሽከርካሪ እና በግዥ ላይ የነበረ ግለሰብ እጅ ከፍንጅ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጸዋል።

በእለቱ 49 ሺህ ሊትር ከጫነው የነዳጅ ቦቴ ሁለት ሺህ ሊትር በመቀሸብ በግብይት ላይ እያሉ እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን አቶ አህመድ ገልጸዋል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review