በምክክር ሂደቱ የጋራ ሀገርን የሚያጸኑ ሃሳቦችን በነጻነት አንስተናል፡- የወላይታ ሶዶ ከተማ የሃገራዊ ምክክር ተሳታፊዎች

You are currently viewing በምክክር ሂደቱ የጋራ ሀገርን የሚያጸኑ ሃሳቦችን በነጻነት አንስተናል፡- የወላይታ ሶዶ ከተማ የሃገራዊ ምክክር ተሳታፊዎች

AMN- ጥቅምት 20/2017 ዓ.ም

በምክክር ሂደቱ የጋራ ሀገርን የሚያጸኑ ሃሳቦችን በነጻነት አንስተናል ሲሉ በወላይታ ሶዶ ከተማ የሃገራዊ ምክክር ተሳታፊዎች ተናገሩ ።

የኢትዮጵያ ሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ሶዶ ከተማ ያስጀመረዉ ምክክር እና የአጀንዳ መለየት ሂደት ሶስተኛ ቀኑን ይዟል ።

ከ96 ወረዳዎች 2ሺ ተወካዮች እየተሳተፉ በሚገኙበት ሂደት ተወካዮች ለሀገር ይበጃሉ ያሏቸዉ አጀንዳዎች ላይ ተወያይተዉ ለይተዋል ።

ለቀጣይ የምክክር ሂደትም የሚወክሏቸዉን አካላት መርጠዋል ።

በክልሉ የሚገኙ 32 ብሄሮችን ወክለዉ እየተሳተፉ የሚገኙ ተወካዮችም ሂደቱ ሀሳቦቻቸዉን በነጻነት ማንሳት የቻሉበትና ዲሞክራሲን የተለማመዱበት መሆኑን ተናግረዋል ።

የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው ከአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ጋር በነበራቸዉ ቆይታ ምክክሩና የአጀንዳ ልየታዉ ከተጠበቀዉ በላይ ዉጤታማ እንደነበር አንስተዋል ።

ከተወካዮች የተሰበሰበዉን አጀንዳም ኮሚሽኑ በቀጣዩ እሁድ አጠናቆ የሚረከብ ይሆናል ሲሉም ገልጸዋል ።

በቀጣይ ከጥቅምት 22 ጀምሮ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ፣የሲቪክ ማህበራትን እና የተቋማት ተወካዮችን ያሳተፉ ዉይይቶች እንደሚደረጉ ተመልክቷል ።

በአለማየሁ አዲሴ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review