በቦሌ ክፍለ ከተማ በህብረተሰብ ተሳትፎ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተደረገባቸዉ የመሰረት ልማት ስራዎች ተመረቁ

You are currently viewing በቦሌ ክፍለ ከተማ በህብረተሰብ ተሳትፎ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተደረገባቸዉ የመሰረት ልማት ስራዎች ተመረቁ

AMN- መስከረም 27/2017 ዓ.ም

በክፍለ ከተማዉ በህብረተሰብ ተሳትፎ የተከናወኑ የውስጥ ለውስጥ የመንገድ ስራዎች የውሀ መውረጃ ቱቦዎች እና የጋራ መፀዳጃ ቤቶችን ጨምሮ የተለያዩ የልማት ስራዎች በህብረተሰብ ተሳትፎ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተመርቀዋል ::

የመሰረት ልማት ስራዎቹ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ተደርጎባቸዋልም ተብሏል ::

በአዲስ አበባ ከተማ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ከ 450 ሚሊዮን ብር ወጭ የተደረገባቸዉ መሰረት ልማቶች መሰራታቸዉን የአዲስ አበባ ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎ እና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ምክትል ኮሚሽነር ወ/ሮ ፀሐይ ኪባሞ ተናግረዋል ::

ኮምሽኑ በ2017 በጀት ዓመት በ750 ሚሊዮን ብር የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን እቅድ መያዙንም ወ/ሮ ፀሐይ ኪባሞ ተናግረዋል ::

በቴዎድሮስ ይሳ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review