በአፋር ክልል የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በጤና ዙሪያ የሚያስከትለውን ተፅዕኖ ለማጥናት እና ምላሽ ለመስጠት የባለሙያዎች ቡድን ተላከ

You are currently viewing በአፋር ክልል የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በጤና ዙሪያ የሚያስከትለውን ተፅዕኖ ለማጥናት እና ምላሽ ለመስጠት የባለሙያዎች ቡድን ተላከ

AMN – ታኀሣሥ 28/2017 ዓ.ም

ጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመሆን የመሬት መንቀጥቀጡ በጤና ላይ የሚያስከትለውን ተፅዕኖ እና መደረግ ያለበትን ጥንቃቄ ለመለየትና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት እንዲያስችል ጥናት ለማድረግ የተለያየ የሙያ ስብጥር ያላቸው የባለሙያዎች ቡድን ወደ ቦታው መላኩን አስታውቋል፡፡

በመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት ከጤና ጋር በተገናኘ በቀጣይ ምን ሊከሰት እንደሚችል ፣ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግና መወሰድ ባለባቸው እርምጃዎች ዙሪያ ጥናት ለማድረግ ከተለያዩ የጤና ሙያ ዘርፎች የተውጣጣ ቡድን በቦታው መድረሱን ከሚኒስቴሩ የተገኘ መረጃ ያመላክታል፡፡

ከክልሉ ጤና ቢሮ እና ከህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቱት ጋር በመሆን አስፈላጊዉን ፈጣን ምላሽ በመስጠት በቅንጅት እየተሰራ መሆኑም ተመላክቷል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review