በደቡብ ኮሪያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ የዴሞክራቲክ ፓርቲው ሊ ጄ-ሚዮንግ አሸነፉ

You are currently viewing በደቡብ ኮሪያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ የዴሞክራቲክ ፓርቲው ሊ ጄ-ሚዮንግ አሸነፉ

AMN – ግንቦት 27/2017 ዓ. ም

ሰሞኑን ሲካሄድ በነበረው የደቡብ ኮሪያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ የዲሞክራቲክ ፓርቲ እጩ ሊ ጄ-ሚዮንግ አሸንፈዋል።

ጠቅላላ ከተሰጡ 95 በመቶ ድምፆች የዲሞክራቲክ ፓርቲው ሊ ጄ-ሚዮንግ 48.86 በመቶ በማግኘት 41.98 በመቶ ድምፅ ካገኙት ተፎካካሪያቸው የፒፕልስ ፓወር ፓርቲ እጩ ኪም ሙን-ሱ በመብለጥ ስልጣኑን ይዘዋል።

የቀድሞ ፕሬዝዳንት ዩን ሱክ-ዮል የስልጣን ዘመናቸው እስከ 2027 እ.ኤ.አ ድረስ የነበረ ቢሆንም ባለፈው ታህሳስ ወር ሃገሪቱ በወታደራዊ አስተዳደር እንድትተዳደር መወሰናቸውን ተከትሎ ከስልጣን በመባረር ክስ ተመስርቶባቸዋል።

ዩን ሱክ-ዮል ሃገሪቱ ለ6 ሰዓታት በወታደራዊ አስተዳደር ስር እንድትቆይ ካደረጓት በሗላ ላለፉት 6 ወራት ሃገሪቱ መረጋጋት ርቋት ቆይታለች።

አዲሱ ፕሬዝዳንት በሃሳብ የተከፋፈለች ሃገር፤ በአሜሪካ ታሪፍ የተጨነቁ ንግዶች እና ውሉ ያልታወቀ የዶናልድ ትራምፕ አጋርነት እንደሚጠብቃቸው ቢቢሲ ዘግቧል።

የምርጫው ውጤት ይፋ ከመደረጉ በፊት ሊ ሃገሪቱን አንድ የማድረግ ራዕይ እንዳላቸው ማስታወቃቸውን ስካይ ኒውስ ዘግቧል።

በሊያት ካሳሁን

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review