ትላንት ማምሻውን በካዛንቺስ ኮሪደር እና መልሶ ማልማት ስራ ላይ ሃገር የማበልፀግ ራእያችንን በመጋራት ሃገር በመገንባት ስራችን የተሳተፉ አካላትን አመስግነናል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

You are currently viewing ትላንት ማምሻውን በካዛንቺስ ኮሪደር እና መልሶ ማልማት ስራ ላይ ሃገር የማበልፀግ ራእያችንን በመጋራት ሃገር በመገንባት ስራችን የተሳተፉ አካላትን አመስግነናል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

AMN – ሚያዝያ 16/2017

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸዉ ባሰፈሩት መልእክት ትላንት ማምሻውን በካዛንቺስ ኮሪደር እና መልሶ ማልማት ስራ ላይ ሃገር የማበልፀግ ራእያችንን በመጋራት በርካታ እንቅልፍ አልባ ሌሊቶችን ፣ እረፍት አልባ የስራ መርሃግር በማሳለፍ አብረዉን ለሰሩ ኮንትራክተሮች፣ አማካሪዎች ፣አመራሮች ፣ሰራተኞች እና ተቋማትን አመስግነናል ብለዋል፡፡

ከነዚህም መካከል ማሽኖቻቸውም በነጻ ለዚህ ስራ ያዋሱ ባለሃብቶችን፣ ስራ ወስደው በፍጥነትና በጥራት ፕሮጀክቶችን በጊዜ በማጠናቀቅ ያስረከቡ ኮንትራክተሮች እና አማካሪዎችን፣ ይህን ስራ ከጅማሮ እስከ ፍጻሜ በፍጹም ታታርነት እና ቅንነት ያስተባበሩ የከተማችን አመራሮችን፣ የግል የመንግስትና የፌደራል ተቋማትን እንዲሁም የህንጻ ባለንብረቶችን ራዕያችንን በመጋራት ሃገር በመገንባት ስራችን ላበረከቱት ጉልህ አስተዋፅዖ ሁሉ በራሴ እና በነዋሪዎቻችን ስም ላመሰግናችሁ እወዳለሁ::

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ ብለዋል ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመልእክታቸዉ፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review