አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሆነው ተሰየሙ

You are currently viewing አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሆነው ተሰየሙ

AMN – መስከረም 27/2017 ዓ.ም

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴን ለኢፌዴሪ ፕሬዚዳንትነት ሰይመዋል።

አዲሱ ፕሬዚዳንት በሁለቱ ምክር ቤቶች ፊት ቀርበው ቃለ-መሐላ የፈፀሙ ሲሆን የቀድሞዋ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ ኃላፊነቱን አስረክበዋቸዋል።

6ኛው የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል።

በዮናስ በድሉ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review