አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ በአቶ ቡልቻ ደመቅሳ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ

You are currently viewing አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ በአቶ ቡልቻ ደመቅሳ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ

AMN – ታኅሣሥ 28/2017 ዓ.ም

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ በአቶ ቡልቻ ደመቅሳ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል፡፡

አቶ ታገሰ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት በቀድሞ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማኝን ሃዘን እገልጻለሁ ብለዋል፡፡

አቶ ቡልቻ በኢትዮጵያ ፖለቲካ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚ መስክ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ለቤተሰቦቻቸው እንዲሁም ለወዳጅ ዘመዶቻቸውም መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review