ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ያላትን አጋርነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ጽኑ ፍላጎት አላት- አምባሳደር ደሊል ከድር

You are currently viewing ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ያላትን አጋርነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ጽኑ ፍላጎት አላት- አምባሳደር ደሊል ከድር

AMN – መጋቢት 19/2017

ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ያላትን ዘርፈ ብዙ ወዳጅነትና ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ደሊል ከድር ገለጹ።

አምባሳደር ደሊል ከድር የሹመት ደብዳቤያቸውን ለደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ አቅርበዋል።

አምባሳደሩ በኢትዮጵያና በደቡብ አፍሪካ መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነትና በፓን-አፍሪካኒዝም መርህ ላይ የተመሰረተውን የረጅም ጊዜ ታሪካዊ የወዳጅነትና ወንድማማችነት እንዲሁም የህዝብ ለህዝብ ትስስርን አውስተዋል።

ኢትዮጵያ ደቡብ አፍሪካ ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ በሚል መርህ የምታደርጋቸውን እንቅስቃሴዎች በማድነቅ በተለይም በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል የነበረው ግጭት መቋጫ እንዲያገኝ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሂደትን በማስተናገድና በማሰናዳት ላደረገችው ጉልህ አስተዋጽኦ በኢትዮጵያ መንግስት ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

አምባሳደር ደሊል በሚኖራቸው ቆይታ የኢትዮጵያን እና የደቡብ አፍሪካን ታሪካዊ ግንኙነት በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በባህል እንዲሁም በህዝብ ለህዝብ ግንኙነት የትብብር ዘርፎች ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ እንደሚሰሩ መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review