AMN-የካቲት 29/2017 ዓ.ም
ከተለያዩ ጤና ተቋማት የተውጣጡ የጤና አመራሮች እና ባለሞያዎች አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬሽን ማዕከልን ጎብኝተዋል::
ዜጎች ጤናቸውን በመጠበቅ ለራሳቸው እና ለሀገራቸው ልማት ተገቢውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ በማዕከሉ ውስጥ ተካትቶ የተገነቡት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረጊያ ሥፍራዎች፣ ከልጆች እስከ አዋቂዎች ላሉ ነዋሪዎች የመዝናኛ ስፍራዎች እንዲሁም ሌሎች መሰል መሰረተ ልማቶች ግንባታ እንዳስደሰታቸው ጎብኚዎቹ መግለጻቸውን የከንቲባ ጽህፈት ቤት መረጃ ያሳያል፡፡