ከአምስቱ የኮሪደር ልማት ስራዎች የአንዱ መጠናቀቁ እና ለህዝብ አገልግሎት ክፍት መሆኑ ከታላላቅ ስኬቶች አንዱ ያደርገዋል፡- የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት

You are currently viewing ከአምስቱ የኮሪደር ልማት ስራዎች የአንዱ መጠናቀቁ እና ለህዝብ አገልግሎት ክፍት መሆኑ ከታላላቅ ስኬቶች አንዱ ያደርገዋል፡- የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት

AMN-ሰኔ 03/2016 ዓ.ም

ከአምስቱ የኮሪደር ልማት ስራዎች የአንዱ መጠናቀቁ እና ለህዝብ አገልግሎት ክፍት መሆኑ ከታላላቅ ስኬቶች አንዱ እንደሚያደርገው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡

ከአራት ኪሎ ራስ መኮንን ድልድይ፤ ከደጎል አደባባይ – ቀይባህር ኮንደሚኒየም እና ከማህሙድ ሙዚቃ ቤት- በቴዎድሮስ አደባባይ ያሉት መንገዶች ድንቅ በሆነ ደረጃ ተሰርተው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸው ማራኪ ገጽታን እና የመገናኛ እንቅስቃሴን እንደሚፈጥሩ ጽህፈት ቤቱ ገልጿል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት ዝናሽ ታያቸው ከከፍተኛ የመንግስት አመራሮች ጋር በመሆን ትናንት ማምሻውን በለሙት ኮሪደሮች ጉብኝት ማካሄዳቸውም ተገልጿል።

የመሰረተ ልማት ሥራዎችን ገምግመዋል፤ የውበትና አረንጓዴ ልማት ሥራዎችን እና የዕድሳትም አድንቀዋል ብሏል ጽ/ቤቱ ።

ይህ ጉብኝት መንግሥት ለተሻሻለ የመንገድ ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ብሎም ለኑሮ ምቹ የሆነ ዘላቂ የመኖሪያ ከባቢን ለመፍጠር ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው ሲል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ባጋራው መረጃ አመልክቷል።

#Addisababa

#Ethiopia

ትክክለኛውን የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዲጂታል ሚዲያ የትስስር አውታሮችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑን!

https://linktr.ee/AddisMediaNetwork

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review