AMN- ጥር 21/2017
ከተለያዩ የአውሮፓ እና አፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ ከ100 በላይ ጎብኚዎች የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል፡፡
በጉብኝታቸውም መጪውን የኢትዮጵያ ትውልድ በሚያስተምር፣ በሚያስተሳስርና ታሪኩን በጠበቀ መልኩ የተገነባውን የዓድዋ ድል መታሰቢያ ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡
የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ግሩም ግርማ እንግዶቹን በመቀበል የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ማስተላለፋቸውን ከዓድዋ ድል መታሰቢያ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡