ዓለም በሳምንቱ

You are currently viewing ዓለም በሳምንቱ
  • Post category:ዓለም

✍️በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በሶማሊያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አድርጓል።

✍️በኢትዮጵያ በርዕደመሬት መለኪያ እስከ 5.8 ሬክተር ስኬል የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን ተከትሎ መንግሥት የርዕደ መሬት በታየባቸው አካባቢዎች የጉዳቱን መጠን አሠሳ የሚያደርግ ቡድን ማሰማራቱን አስታውቋል።

✍️በሲዳማ ክልል ባጋጠመ የመንገድ የትራፊክ አደጋ ከ 70 በላይ ሰዎች መሞታቸውን ፖሊስ አስታውቋል።

✍️የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት በመላው ዓለም በድምቀት ተከብሯል።

✍️የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጂሚ ካርተር በ100 አመታቸው ህይወታቸው አልፏል።

✍️አስከፊ አደጋ የደረሰባት ደቡብ ኮሪያ በቦይንግ አውሮፕላኖች ላይ ፍተሻ እንዲደረግ ማዘዟ ተነግሯል።

✍️ተሰናባቹ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለዩክሬን የ2.5 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ አፅድቀዋል፡፡

✍️አዲሱ የሶሪያ መሪና የዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በደማስቆ ተወያይተዋል።

✍️እስራኤል በጋዛ በሚገኙ ጤና ተቋማት ላይ ከምታደርገው ተደጋጋሚ ጥቃት እንድትቆጠብ የአለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሀኖም አሳስበዋል።

✍️ከስልጣን የታገዱት የደቡብ ኮሪያው ፕሬዝደንት ዩን ሱክ ዬኦል እንዲታሰሩ ፍርድ ቤት የወሰነባቸው ቢሆንም የሀገሪቱ ባለስልጣናት ፕሬዝደንቱን በቁጥጥር ስር ለማዋል ያደረጉት ጥረት ሳይሳካ መቅረቱ ተገልጿል።

✍️እስራኤል ሀውቲዎች የሀማስ እና ሄዝቦላ እጣፋንታ ሊያጋጥማቸው ይችላል ስትል አስጠንቅቃለች።

✍️ዩክሬን እና ሩሲያ ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ ከፍተኛ የተባለውን የጦር እስረኞች ልውውጥ አድርገዋል።

✍️ሩሲያ በዩክሬን በኩል ለአውሮፓ ሀገራት ነዳጅ መላክ ማቆሟን አስታውቃለች።

✍️ሩሲያ የአሜሪካ ሰራሽ ሚሳይሎችን ማክሸፏን አስታውቃለች።

✍️አይቮሪኮስት የፈረንሳይ ወታደሮች ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ አስተላልፋለች።

✍️በአሜሪካ ኒውኦርሊያንስ አንድ ግለሰብ አዲስ አመትን ለማክበር በተሰባሰቡ ሰዎች ላይ በመኪና ባደረሰው ጥቃት ከ14 በላይ ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች ቆስለዋል።

✍️እስራኤል የተቋረጠውን የጋዛ ተኩስ አቁም ድርድር ዳግም ለማስጀመር ልኡኳን ወደ ዶሃ ልትልክ መሆኑ ተነግሯል።

✍️አሜሪካ ለእስራኤል 8 ቢሊዮን ዶላር የጦር መሳሪያ ለመሸጥ ማቀዷን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ተናግረዋል።

✍️ቻይና የኮቪድ መረጃን ይፋ እንድታደርግ የዓለም ጤና ድርጅት አሳስቧል።

AMN-ታህሣሥ 27/2017 ዓ.ም

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review