የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸዉ ባሰፈሩት መልእክት ዛሬ ከከተማችን ነዋሪዎች የተነሱ ጥያቄዎች በምክር ቤት አባላት አማካኝነት ቀርበው ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተናል ብለዋል፡፡
ህዝባችንን ማዳመጥ እና ለሚነሱ ጥያቄዎች ፈጣን እና ተግባራዊ ምላሽ መስጠት የአመራራችን መገለጫ፣ የአገልግሎታችን አንዱ እና ትልቁ አካል በመሆኑ ከነዋሪዎቻችን ለተነሱ ጥያቄዎች እንዲሁም ሃሳቦች በሙሉ ምላሽ እና ማብራሪያዎችን ሰጥተናል።
ለተነሱልን ጥያቄዎች የተሰጡ ማብራሪያዎችን እና ዝርዝር መረጃዎችን በተለያዩ ሚዲያዎች እንዲሁም በዚህ ገፅ የምንለቅ ይሆናል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡