የመንግስት የልማት ድርጅቶች አትራፊ እና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ እየተሰራ ነው፡-የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን

You are currently viewing የመንግስት የልማት ድርጅቶች አትራፊ እና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ እየተሰራ ነው፡-የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን

AMN – ጥር- 24/2017 ዓ.ም

የመንግስት የልማት ድርጅቶችን የተሟላና ዘመናዊ አገልግሎትን ከመስጠት ባለፈ ይበልጥ አትራፊ እና ተወዳዳሪ እንደሆኑ እየተሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን ገለጸ።

ባለስልጣኑ በስሩ የሚገኙ 7 የመንግስት የልማት ድርጅቶችን የ2017 የ6 ወር የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ግምገማና ውይይት አካሄዷል።

የመንግስት ልማት ድርጅቶችን ይበልጥ ውጤታማ ፣ አትራፊ እና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አባወይ ዮሐንስ ተናግረዋል።

ባለፉት 6 ወራት እና ከዛ ቀደም በተደረገው ጠንካራ ድጋፍና ክትትል ኪሳራ ውስጥ የነበሩ የመንግስት የልማት ድርጅቶችን ከኪሳራ በማውጣት ትርፋማ እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏልም ብለዋል አቶ አባወይ።

የኤግዚቢሽን ማዕከልና ገበያ ልማት ድርጅት ፣ የአዲስ አበባ የኮንስትራክሽን ዲዛይን ፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት ፣ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ፣ ከነማ ፋርማሲዎች ድርጅት ፣ የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን ፣ ሲኒማ ቤቶች አስተዳደር አስተዳደር እና የንግድ ስራዎች ድርጅትን የልማት ድርጅቶችን የተቋማቸውን የአፈጻጸም ሪፖርት አቅርበው ውይይት ተካሄዷል።

የመንግስት የልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን በአዋጅ ቁጥር 84/2016 አንቀጽ 40 የተቋቋመ ሲሆን የመንግስት የልማት ድርጅቶችን የመከታተል የመቆጣጠር እና የመደገፍ ኃላፊነት ያለበት ተቋም መሆኑም ተጠቁሟል።

በዳንኤል መላኩ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review