የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር እና በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የከተሞችና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር) ከዘረዘሯቸው በክልሉ በማህበራዊ ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች ዋና ዋና ነጥቦች፤

You are currently viewing የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር እና በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የከተሞችና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር) ከዘረዘሯቸው በክልሉ በማህበራዊ ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች ዋና ዋና ነጥቦች፤

-በጤናው ዘርፍ ህፃናት ላይ የተሰራው ሥራ በተለይም የቀዳማይ ልጅነት መርሐ-ግብር በሚል ከቅድመ ወሊድ ጀምሮ ለእናቶች እንክብካቤ የማድረግ እና ህፃናት ከተወለዱም በኋላ ዘርፈ ብዙ ክትትል በማድረግ ህፃናትን የቀጣዩ ሀገር ተረካቢ ትውልድ የማድረግ ሥራ ውጤት የተገኘበት ነው፤

-የቀዳማይ ልጅነት መርሐ-ግብር ከአዲስ አበባ ጀምሮ በክልሎች እየሰፋ መጥቶ በአማራ ክልል ከተሞችም እየተከናወነ ያለ ሥራ ነው፤

-በትምህርት ዘርፍም የትምህርት ጥራትን የማረጋገጥ እና የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ውጤታማ ሥራዎች ተሰርተዋል፤

-ለወጣቶች መዋያ እና መዝናኛ ሥፍራዎች፣ ሀሳባቸውን የሚያንሸራሽሩበት ቦታዎች ላይ እየተከናወነ ያለው ተግባር ይበል የሚያሰኝ ነው፤

-ቀደም ሲል ወጣቶች ሀሳባቸውን ወደ ውጤት፣ ወደ ቢዝነስ የሚቀይሩበት ዕድል ያልነበረ ሲሆን፣ አሁን ይሄ ዕድል ተመቻችቷል፤

-በሀገር ደረጃ ወጣቶች ሀሳባቸውን ወደ ውጤት ቀይረው እዛ ሀሳባቸው ላይ ኢንቨስት ከሚያደርጉ ባለሀብቶች ጋር የሚገናኙባቸው የተለያዩ ቦታዎች አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ ክልሎች ተቋቁመዋል::

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review