AMN- የካቲት 7 /2017 ዓ. ም.
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በ4ኛ ዓመት 8ኛ መደበኛ ስብሰባው ሁለት አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አስተላልፏል፡፡
1ኛ. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ሰራተኞች አዋጅን ካቢኔው ተወያይቶ ለአዲስ አበባ ምክር ቤት እንዲቀርብ ወሳኔ አሳልፏል፡፡
2ኛ. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቴክኒክ እና ሞያ ማሰልጠኛ ተቋማትን እንደገና ለማቋቋም በቀረበዉን ሪቂቀ አዋጅ ላይ ተወያይቶ ለአዲስ አበባ ምክር ቤት እንዲቀርብ ውሳኔ ማሳለፉን ከከንቲባ ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡