የአፍሪካ የመከላከያ ሚኒስትሮች የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደርን ጎበኙ

You are currently viewing የአፍሪካ የመከላከያ ሚኒስትሮች የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደርን ጎበኙ

AMN – ጥቅምት 7/2017 ዓ.ም

የአፍሪካ የመከላከያ ሚኒስትሮች የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደርን/ኢመደአን/ ጎብኝተዋል።

ሚኒስትሮቹ ጉብኝት ያደረጉት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ከሚገኘው የአፍሪካ የመከላከያ የሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን ነው።

ለመከላከያ ሚኒስትሮቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ያደረጉት የኢመደአ ም/ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ አስቴር ዳዊት፣ ተቋሙ ኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነቷንና ዲጂታል ሉዓላዊነቷን ለመጠበቅ የሚያስችል አይበገሬ የሳይበር አቅም ለመገንባት እያደረገ ስላለው ስራ ሰፊ ገለጻ ማድረጋቸውን ከአስተዳደሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review