AMN – መስከረም 23/2017 ዓ.ም
የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የ2017 የኢሬቻ በአልን አስመልክቶ ከክፍለ ከተማው ነዋሪዎች ጋር የማጠቃለያ ውይይት አካሂዷል።
የኢሬቻ በዓል የተስፋ፣ የይቅር ባይነት፣ የወንድማማችነት እና የአንድነት ተምሳሌት ነው ያሉት የየካ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብርሃኑ ረታ፣ ይህንንም ለዘመናት የኖረውን እሴት በመጠቀም የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት ልናውለው ይገባል ብለዋል።
በዓለሙ ኢላላ