የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ እድገት የሚያደርጉትን ድጋፍ ኢትዮጵያ ታደንቃለች፡-አቶ አህመድ ሺዴ

You are currently viewing የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ እድገት የሚያደርጉትን ድጋፍ ኢትዮጵያ ታደንቃለች፡-አቶ አህመድ ሺዴ

AMN- ጥቅምት 13/2017 ዓ.ም

የዓለም ባንክ እና የዓለም የገንዘብ ተቋም ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ እድገት የሚያደርጉትን ድጋፍ ኢትዮጵያ እንደምታደንቅ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ ገለጹ፡፡

ኢትዮጵያ አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ እየተካሄደ ባለው የጂ 24 የገንዘብ ሚኒስትሮችና የባንክ ገዥዎች ስብሰባ እየተሳተፈች ነው ፡፡

በገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሺዴ የተመራ ከፍተኛ የኢትዮጵያ ልዑኩ ከውጭ ምንዛሪ ጋር በተያያዘ የምታራምደውን አቋም አብራርተዋል።

ሀገራት ከወለድ ጫና ተላቀው ተመጣጣኝ በሆነ ወለድ ገንዘብ ማግኘት እንዳለባቸው ሚኒስትሩ አሳስበዋል ።

በዚህ ረገድ የዓለም ባንክ እና አይ ኤምኤፍ ትብብር ማድረግ እንዳለባቸው ማስገንዘባቸውን ከገንዘብ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review