ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸዉ ባሰፈሩት መልእክት አራተኛውን እና የክረምት በጎ ፍቃድ ስራ አካል የሆነውን የገጠር ኮሪደር ልማት ስራ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ሁልባረግ ወረዳ ወራበት ሻማ ቀበሌ ሞዴል የአርሶ አደሮች የመኖሪያ መንደር ግንባታ አስጀምረናል ብለዋል፡፡
እነዚህ መኖሪያዎች ተገንብተው ሲጠናቀቁ የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘዬ የሚቀይሩ እና ጤናማ ህይወትን የሚያላብሱት ናቸው።
በሌላ በኩል በዞኑ በነበረን ቆይታ የግሉ ዘርፍ በአግሮ ኢንደስትሪ ላይ ያለውን ተሳትፎ ተመልክተናል። እንደማሳያ አቶት የተቀናጀ አግሮ ኢንደስትሪን ተዘዋውረን ተመልክተናል። እንዲህ ያሉት ስራዎች በሌማት ትሩፋት ውጤት ለማስመዝገብ የተጀመረውን ተግባር ከግብ ለማድረስ በጎ ጅምሮች በመሆናቸው ሊበረታቱ ይገባል ሲሉ ገልፀዋል፡፡