ለ6ኛ ዙር የሰለጠኑ 2ሺ 74 ደንብ አስከባሪ ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮችን ማስመረቃቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ

You are currently viewing ለ6ኛ ዙር የሰለጠኑ 2ሺ 74 ደንብ አስከባሪ ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮችን ማስመረቃቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ

AMN-ግንቦት 30/2017 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት አዲስ አበባ እጅግ በጣም ፈጣን ለውጥ እያስመዘገበች የምትገኝ ከተማ መሆኗን ገልፀው ለነዋሪዎቿ እና ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች ተመራጭ ትሆን ዘንድ በልማቱ ብቻ ሳይሆን በሰላም፣ ደህንነት፣ ህግ እና ስርዓትን በማስከበር ረገድም ውጤታማ ስራዎች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል፡፡

ዛሬ የተመረቃችሁ እና ስምሪት የወሰዳችሁ የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮቻችን፣ ዋነኛው የሰላም ባለቤት ከሆነው የከተማችሁ ህዝብ ጋር በመሆን የተጣለባችሁን ታላቅ እምነት ይዛችሁ በንድፈ ሀሳብና በተግባር በቀሰማችሁት እውቀትና ክህሎት ህዝባችሁን በቅንነት፣ በታማኝነትና በአገልጋይነት መንፈስ ማገልገል ይጠበቅባችኋል ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review