ሕብረተሰቡ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ጥያቄዎቹን እንዲያቀርብ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ጥሪ አቀረበ

You are currently viewing ሕብረተሰቡ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ጥያቄዎቹን እንዲያቀርብ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ጥሪ አቀረበ

AMN- መጋቢት 2/2017 ዓ.ም

ሕብረተሰቡ በትምህርት፣ በጤና፣ በኢኮኖሚ ጉዳዮችና አምራች ዘርፎች ላይ ጥያቄዎቹንና ማብራሪያ የሚሹ ጉዳዮችን እንዲያቀርብ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ጥሪ አቅርቧል፡፡

በዚሁ መሠረት ሕብረተሰቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የማኅበራዊ ትሥሥር ገጾች አማካኝነት ጥያቄዎቹን መላክ እንደሚችል ተገልጿል፡፡

ለሚቀርቡ ጥያቄዎችም የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡበት ጽሕፈት ቤቱ አስታውቋል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review