ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ሁለተኛው የብራዚል-አፍሪካ የምግብ ዋስትና፣ ረሃብን መዋጋት እና የገጠር ልማት ጉባኤ በብራዚሏ ዋና ከተማ ብራዚሊያ መካሄድ መጀመሩን ገለጹ

AMN ግንቦት 12/2017 ዓ.ም

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸዉ ባሰፈሩት መልእክት ሁለተኛው የብራዚል-አፍሪካ የምግብ ዋስትና፣ ረሃብን መዋጋት እና የገጠር ልማት ጉባኤ በብራዚሏ ዋና ከተማ ብራዚሊያ መካሄድ መጀመሩን ገልጸዋል፡፡

‎መድረኩ የግብርና ምርትን እድገት፣ የገጠር ልማትንና የምግብ ዋስትናን ማሻሻል ላይ ትኩረት አድርጓል።

‎ግብርናን በተሻለ መንገድ የሚመሩ የጥናትና ምርምር፣ አዳዲስና በቴክኖሎጅ የታገዙ አሰራሮችን የሚያሳልጡ ተቋማት ግንባታ በዘርፉ ከፍ ያለ እመርታ የሚያመጡ ናቸው።

‎ኢትዮጵያ በፖሊሲ የተደገፈ መሰረታዊ የለውጥ ስራዎችን በመተግበር የግብርናውን ዘርፍ ከፍ ባለ እመርታ ላይ ለማስገኘት የሰራችውንና እየሰራች ያለውን ተሞክሮ በጉባዔው ታቀርባለች የሌሎችንም ትጋራለች።

‎በመድረኩ የእውቀት ሽግግር እና የደቡብ-ደቡብ ትብብርን በመጠቀም የምግብ ስርዓታችንን ሊያጠናክሩ የሚችሉ የመስክ ምልከታዎችን፣ የልምድ ልውውጦችንና ስምምነቶችን ማከናወን ቀጥለናል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review