‎በመዲናዋ በተሰራው ቅንጅታዊ ስራ የወንጀል ምጣኔ እና የደንብ ጥሰቶች ቀንሰዋል-የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ

You are currently viewing ‎በመዲናዋ በተሰራው ቅንጅታዊ ስራ የወንጀል ምጣኔ እና የደንብ ጥሰቶች ቀንሰዋል-የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ

AMN-ሚያዝያ 18/2017 ዓ.ም

‎በመዲናዋ በተሰራው ቅንጅታዊ ስራ የወንጀል ምጣኔ እና የደንብ ጥሰቶች መቀነሳቸውን የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ገለጹ።

‎የአዲስ አበባ ሰላምና አስተዳደር ቢሮ እና ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የበጀት ዓመቱን 9ወራት እቅድ አፈጻጸም እየገመገሙ ነው።

‎የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ እንደገለጹት፤ በከተማዋ በተሰራው ቅንጅታዊ ስራ የወንጀል ምጣኔ እና ህገወጥ ተግባራት እንዲቀንሱ ሆነዋል።

‎ህዝቡን ያሳተፈ የጸጥታ አደረጃጀት እንዲኖር በማድረግም ህዝቡን የሰላም ባለቤት በማድረግ የህግ የበላይነት እንዲሰፍን ስለመደረጉም አንስተዋል።

‎የተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች እና ሌሎች ተግባራት በየአካባቢው እንዲከስሙ ከማድረግ አንጻር የሰላም ሰራዊት የማይተካ ሚና እየተወጣ መሆኑንም ገልጸዋል።

‎በከተማዋ አስተማማኝ እና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ የሰላም ሰራዊቱ ሚናውን እየተወጣ ይገኛልም ብለዋል።

‎በዚህም የሰላም ሰራዊትን በሰው ሀይል ለማደራጀት ያስችል ዘንድ በቅርቡ ከ33ሺህ በላይ የሰላም ሰራዊት አባላት ሰልጥነው እንዲወጡ መደረጉን ተናግረዋል።

‎በአጠቃላይ ህብረተሰቡን የሰላም ባለቤት በማድረግ በተሰራው ስራ ህገወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር፣ ሀሰተኛ የገንዘብ ዝውውር እና ወንጀል ፈጻሚ ጸጉረ ልውጦችንም መከላከል መቻሉን አንስተዋል።

በሄለን ጀንበሬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review