በስልጤ ዞን ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ እየተካሄደ ነው

You are currently viewing በስልጤ ዞን ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ እየተካሄደ ነው

AMN – ሚያዝያ 06/2017

በስልጤ ዞን ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ እና ዞን አቀፍ የኢንቨስትመንት ፎረም በወራቤ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡

‎በፎረሙ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ብልካን ጨምሮ ሌሎች የዞን፣የወረዳና የከተማ አስተዳደሮች ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችና ባለሀብቶች ተሳትፈውበታል።

‎በዞኑ አጠቃላይ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች፥ እምቅ የኢንቨስትመንት አቅሞች እና በዘርፉ በሚታዩ ማነቆዎችና የትኩረት መስኮች ላይ ከባለሀብቱና ከሌሎችም ባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር እንደሚካሄድ ከዞኑ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ያገኘነዉ መረጃ ያሳያል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review