AMN-የካቲት 15/2017 ዓ.ም
በሸገር ከተማ የሕዝብ ኮንፍረንስ መካሄድ ጀምሯል።
በኮንፍረንሱ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)፣ በሸገር ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አለማየሁ ቱሉ እና የኦሮሚያ ንግድ ቢሮ ኃላፊ መሠረት አሰፋ መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
በሕዝብ ኮንፍረንሱ ላይ ከከተማዋ ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ ነዋሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ሀገር አቀፍ የሕዝብ ኮንፍረንስ ከዛሬ ጀምሮ በ25 የኢትዮጵያ ዋና ዋና ከተሞች እንደሚካሄድ ብልፅግና ፓርቲ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል።