በተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ የተሰማሩ የኢትዮጵያ ፖሊስ መኮንኖች ለጀግኖች ማዕከል ከግማሽ ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ

You are currently viewing በተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ የተሰማሩ የኢትዮጵያ ፖሊስ መኮንኖች ለጀግኖች ማዕከል ከግማሽ ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ

AMN – ጥር 13/2017 ዓ.ም

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት በደቡብ ሱዳን ሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ የተሰማሩ የኢትዮጵያ ፖሊስ መኮንኖች ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጀግኖች ማዕከል 6 መቶ 34 ሺህ 5 መቶ ብር ድጋፍ አድርገዋል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል፣ ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ጀግኖች ማዕከል የተደረገው ድጋፍ ለሌሎችም በትምህርትነት የሚወሰድ መሆኑን ተናግረው ለተደረገው ድጋፍ በማኔጅመንቱና በፖሊስ ሠራዊቱ ስም ምስጋና ማቅረባቸውን ከፌዴራል ፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review