በትናንትናው ዕለት ይፋ የተደረገው ኢ-ፓስፖርት፤-

You are currently viewing በትናንትናው ዕለት ይፋ የተደረገው ኢ-ፓስፖርት፤-

👉 ነባሩ ፓስፖርት የአገልግሎት ጊዜው እስኪያበቃ ጥቅም ላይ መዋሉን ይቀጥላል፣

👉የዕድሳት ጊዜው ሲደርስ በኢ-ፓስፖርት ይተካል፣

👉እድሜአቸው ከ25 አመት በላይ ለሆኑ የአገልግሎት ጊዜው 10 አመት ነው፣

👉14 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈት አገልግሎቱን ለመስጠት ዝግጅት ተጠናቋል፣

👉ከአንድ ነጥብ 5 ሚልየን በላይ ኢ-ፓስፖርት ታትሞ ተዘጋጅቷል፣

👉ከፓስፖርት በተጨማሪ ከ10 በላይ የጉዞ ሰነዶችን እንዲዘምኑ ማድረግ ተችሏል፣

👉አዲሱ የኢ-ፓስፖርት በነበረው ዋጋ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ ይሆናል።

👉ተቋሙ ሪፎርም ማድረግ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የጉዞ ሰነዶችን ዘመናዊ ለማድረግ እየሰራ ቆይቷል፣

👉ሀገራችን ለፓስፖርት ህትመት የምታወጣውን የውጭ ምንዛሬ በማስቀረት የሚኖረው ፋይዳ ጉልህ ነው፣

👉ከዚህ በፊት አገልግሎት እየተሰጠ የቆየው 20 ዓመት ባለፈው ቴክኖሎጂ ነው፣

👉ይህንን ቴክኖሎጂ በሀገር ውስጥ መገንባት መቻሉ ትልቅ ድል ነው፣

👉አዲሱ ቴክኖሎጂ ግን ደንበኞች ባሉበት ፓስፖርታቸውን በፍጥነት ማግኘት እንዲችሉ ያደርጋል፣

👉ከዚህ በፊት የሚያጋጥሙ የደህንነት ችግሮችን ሙሉ በሙሉ ይቀርፋል፣

👉አዲሱ ኢ-ፓስፖርት እስከአሁን ኢትዮጵያ ካላት ፓስፖርት በአይነቱና በደረጃው እጅግ ከፍ ያለ እና አለም የደረሰበት የመጨረሻው ቴክኖሎጅን በመጠቀም የተዘጋጀ የጉዞ ሰነድ ነው።

ምንጭ-የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review