በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ስራዎች የሚያስደንቁ መሆናቸዉን የአርሜንያ ም/የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታኒያን ገለጹ

You are currently viewing በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ስራዎች የሚያስደንቁ መሆናቸዉን የአርሜንያ ም/የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታኒያን ገለጹ

AMN ሰኔ 3/2017

በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ስራዎች የሚያስደንቁ መሆናቸውን የአርሜንያ ሪፐብሊክ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታኒያን ገለጹ፡፡

ኢትዮጵያ እና አርመኒያ ያላቸው የረጅም ጊዜ ግንኙነትን ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት እንደሚከናወኑም ገልጸዋል።

የአርሜንያ ሪፐብሊክ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታኒያን ዛሬ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡

ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታኒያን እንደገለጹት፤ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የተመለከቷቸው ትልልቅ የልማት ስራዎችና ግንባታዎች የሚያስደንቁና የከተማዋን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ ሰው ወዳድ፣ እንግዳ ተቀባይ ነው ያሉት ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኮስታኒያን፤ በኢትዮጵያ ቆይታቸው መልካም ጊዜ ማሳለፋቸውን ገልጸዋል፡፡

አርመኒያ ትምህርት፣ቴክኖሎጂ እና ጤና ከፍተኛ እውቅና ያገኘችባቸው ዘርፎች መሆናቸውን ጠቁመው፤ በእነኚህ እና በሌሎችም ዘርፎች ያላትን ልምድ ለኢትዮጵያ ለማካፈል ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል፡፡

በሌላ መልኩም በዲጂታላይዜሽን እና የመንግስት አገልግሎትን በቴክኖሎጂ ከመደገፍ አኳያም ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ ለመሥራት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ እና አርመኒያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናክር እንደሚሰሩም ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ቫሃን ኮስታኒያን ተናግረዋል፡፡

አርመኒያ ከኢትዮጵያ ጋራ ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ጠቁመው፤ በኢትዮጵያ በኩልም ይህንን ቁርጠኝነት መመልከታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review