በአዲስ አበባ የገበያ ማዕከል በተደረገ ፍተሻ በርካታ በኮንትሮባንድ የገቡ የሞባይል ስልኮች ተያዙ

You are currently viewing በአዲስ አበባ የገበያ ማዕከል በተደረገ ፍተሻ በርካታ በኮንትሮባንድ የገቡ የሞባይል ስልኮች ተያዙ
  • Post category:ቢዝነስ

AMN-ኅዳር 13/2017 ዓ.ም

በአዲስ አበባ የገበያ ማዕከል በተደረገ ፍተሻ በርካታ በኮንትሮባንድ የገቡ የሞባይል ስልኮች መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ፖሊስ ባደረገው የክትትልና የጥናት ተግባር በርካታ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን መያዙን ገልጿል፡፡

የፖሊስ መምሪያው የወንጀልና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ዲቪዥን ኃላፊ የሆኑት ዋና ኢንስፔክተር ተስፋዬ ለማ እንደገለፁት ህዳር 12 ቀን 2017 ዓ/ም በክ/ከተማው ወረዳ 8 ልዩ ቦታው አዲስ አበባ የገበያ ማዕከል ውስጥ በሚገኝ የንዋየ ቅዱሳትና ሞባይል ቀፎ መሸጫ ሱቅ ላይ በተደረገ ፍተሻ በርካታ የሞባይል ቀፎዎችን ከነ ቻርጀሮቻቸው ተይዘዋል፡፡

በፍተሻውም 301 የስማርት ስልክ ቀፎዎች፣ 61 ኖርማል በተን ሞባይል ስልክ ቀፎዎች እንዲሁም 29 የሞባይል ቻርጅሮች ይገኙበታል ብለዋል፡፡

የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ የተያዘበት አንደኛው ሱቅም የንዋየ ቅዱሳት መሸጫ ቢሆንም ከውስጡ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች የሚከማቹበት መሆኑንም ማረጋገጥ እንደተቻለ የገለፁት ኃላፊው ከተሰጣቸው የንግድ ፈቃድ ውጪ በንዋየ ቅዱሳት መሸጫ ሱቅ ስም የሀገርን ኢኮኖሚ በእጅጉ የሚጎዳ ተግባር ለመፈፀም የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችም ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ኃላፊው አሳስበዋል፡፡

መሰል ህገ-ወጥ ተግባራትን ለመቆጣጠር የፀጥታ አካላት የሚያከናውኑትን ሥራ ህብረተሰቡ መረጃ በመስጠት እንዲተባበር መልዕክት መተላለፉን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review