‎በአዲስ አበባ 5ኛው ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ ተከፈተ

You are currently viewing ‎በአዲስ አበባ 5ኛው ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ ተከፈተ

AMN-መጋቢት 29/2017

‎የአዲስ አበባ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ከመጋቢት 1 እስከ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ሲያካሂድ የቆየው የ5ኛ ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ ሰነድ ሽያጭ የመክፈቻ መርሐ-ግብር ተካሂዷል።

‎በቦሌ ክፍለ ከተማ የተካሄደው 5ኛው ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ የመክፈቻ መርሐ-ግብር ለ5 ቀናት እንደሚቆይ ተገልጿል።

‎ ‎

‎በአጠቃላይ 427 ፕሎቶች (የተዘጋጁ ቦታዎች) የተሰናዱበት 5ኛው ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ መካከል ዛሬ 86 ፕሎቶችን የያዙ 5 ክፍለ ከተሞች ማለትም፣ የካ ፣ ቂርቆስ ፣ ጉለሌ ፣ አራዳ እና ለሚ ኩራ ላይ ነው የተከፈተው።

‎በጨረታ መክፈቻው የአዲስ አበባ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሲሳይ ጌታቸውን ጨምሮ ሌሎች የቢሮው የስራ ኃላፊዎች፣ ተጫራቾች እና ህጋዊ ወኪሎች ተገኝተዋል።

በሄለን ጀንበሬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review