በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች እና አሰልጣኝ ለመምረጥ እጩዎች ቀረቡ

AMN-ግንቦት 7/2017 ዓ.ም

የውድድር ዓመቱ መገባደጃ ላይ የሚገኘው የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ለመምረጥ ስምንት እጩዎችን አቅርቧል፡፡

ከስምንቱ እጩዎች ውስጥ ሊቨርፑል ሞሃመድ ሳላህ ፤ ቨርጅል ቫንዳይክ እና ሪያን ግርቨንበርችን በማስመረጥ ቅድሚያውን ወስዷል፡፡

የኖቲንግሃም ፎረስቶቹ ሞርጋን ጊብስ ኋይት እና ክሪስ ዉድ ፤ ዴክለን ራይስ ከአርሰናል ፤ አሌክሳንደር ኢሳክ ከኒውካስትል እንዲሁም ብሪያን ምቤሞ ከብሬንትፎርድ ሌሎች እጩዎች ናቸው፡፡

በተመሳሳይ የአሰልጣኞችም እጩዎች ይፋ ሆነዋል፡፡

በዚህም አርነ ስሎት ከሊቨርፑል ፤ ኤዲ ሃው ከኒውካስትል ዩናይትድ ፤ ቶማስ ፍራንክ ከ ብሬንትፎርድ ፤ ኑኖ ስፕሪቶ ሳንቶ ከኖቲንግሃም ፎረስት እንዲሁም ቪቶር ፔሬራ ከወልቭስ በእጩነት የቀረቡ አሰልጣኞች ናቸው፡፡

በሸዋንግዛው ግርማ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review