AMN-መጋቢት 07/2017 ዓ.ም
የ2025 የሴኡል ማራቶን በሁለቱም ፆታ በኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸናፊነት ተጠናቋል።
በወንዶች የ2025 ሴኡል ማራቶን አትሌት ሀፍቱ ተክሉ በ2:05.37 በመግባት በአንደኝነት አሸንፏል።

በሴቶች ምድብ አትሌት በቀለች ጉደታ በ2:21.35 በአንደኛ ደረጃ ፣አትሌት ፍቅርተ ወረታ ሁለተኛ እንዲሁም አትሌት መስታውት ፍቅር ሶስተኛ ደረጃ በመያዝ ተከታትሎ በመግባት ማሸነፋቸውን የአትሌቲክስ ፌደሬሽን መረጃ ያሳያል።