በ90 ቀናት የበጎ ፈቃድ መርሐ-ግብር 185 ሺህ የመዲናዋ ነዋሪዎች ነፃ የህክምና አገልግሎት እንደሚያገኙ ተገለፀ

You are currently viewing በ90 ቀናት የበጎ ፈቃድ መርሐ-ግብር 185 ሺህ የመዲናዋ ነዋሪዎች ነፃ የህክምና አገልግሎት እንደሚያገኙ ተገለፀ
  • Post category:ጤና

AMN- ሰኔ 15/2017 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ እና በስሩ የሚገኙ ጤና ተቋማት የ90 ቀናት እቅድ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል እየተካሄደ ይገኛል።

እስከ ጳጉሜ አምስት ቆይታ በሚኖረው መርሐ-ግብር፣ በከተማ አቀፍ ደረጃ 185 ሺህ የመዲናዋ ነዋሪዎች የደም ግፊት፣ የስኳር፣ የዓይንና የማህፀን ምርመራና ህክምና የሚያገኙ ይሆናል።

በዚህም 5 ሺህ ዩኒት ደም ለማሰባሰብ ውጥን ስለመያዙ በማስጀመሪያ መርሐ-ግብሩ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሃንስ ጫላ ገልፀዋል።

እንደ ሌሎች ዘርፎች ሁሉ በጤናው ዘርፍ ሰው ተኮር ተግባራት እየተበራከቱ ስለመምጣታቸው ያነሱት ኃላፊው፣ የአቅመ ደካሞች ቤት እድሳት እና ማዕድ ማጋራትን የመሳሰሉ ተግባራት በስፋት እንደሚከናወኑም አስታውቀዋል።

የዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል በዛሬው መርሐ-ግብር ለ300 ሰዎች ነፃ የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን፣ 300 ዩኒት ደም ለመሰብሰብም ማቀዱ ተመላክቷል።

በአጠቃላይ በሶስቱ ወራት ሶስት ሺህ ዜጎች በሆስፒታሉ የመርሐ-ግብሩ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል።

በመቅደስ ደምስ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review