ኢትዮጵያና ሞሪታኒያ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ

You are currently viewing ኢትዮጵያና ሞሪታኒያ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ

AMN – ህዳር 2/2017 ዓ.ም

የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) ከሞሪታኒያ እስላማዊ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ እና የትብብር ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሞሐመድ ሳሌም ኦድ መርዛውግ ጋር ተወያይተዋል፡፡

ሚኒስትሩ በሩሲያ ሶቺ ከተማ እየተካሄደ ካለው የሩሲያ-አፍሪካ አጋርነት ፎረም የሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን ከሞሪታኒያ አቻቸው ጋር የተለያዩ አህጉራዊ የጋራ ጉዳዮችን ያካተተ ውይይት አድርገዋል፡፡

በውይይታቸውም የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ትብብር ለማጠናከር መስማማታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review