ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን ትብብራቸውን ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማሸጋገር ተስማሙ

You are currently viewing ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን ትብብራቸውን ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማሸጋገር ተስማሙ

AMN-የካቲት 28/2017 ዓ.ም

ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ ለማሸጋገር ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ረመዳን መሐመድ አብደላ ጎክ ጋር በጁባ ተወያይተዋል።

ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው፣ የኢትዮጵያ እና የደቡብ ሱዳንን የሁለትዮሽ ትብብር ለማጠናከር እና ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማሸጋገር ከስምምነት ደርሰዋል።

የሀገራቱን የኢኮኖሚ ትብብር እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር የበለጠ ለማጎልበት እንደሚሰሩም መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review