ዦ ጎሜዝ ለረጅም ጊዜያት ከሜዳ ሊርቅ ይችላል ተባለ፤

You are currently viewing ዦ ጎሜዝ ለረጅም ጊዜያት ከሜዳ ሊርቅ ይችላል ተባለ፤
PLYMOUTH, ENGLAND - FEBRUARY 09: Joe Gomez of Liverpool looks dejected as he leaves the pitch with a injury during the Emirates FA Cup Fourth Round match between Plymouth Argyle and Liverpool at Home Park on February 09, 2025 in Plymouth, England. (Photo by Dan Mullan/Getty Images)

AMN-የካቲት 11 ቀን 2017 አ.ም

በእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ 4ኛ ዙር ሊቨርፑል ሳይጠበቅ በፕሌማውዝ ተሸንፎ ከውድድሩ መሰናበቱ የሚታወቅ ነው፡፡

በእለቱ ጨዋታ የሊቨርፑሉ ተከላካይ ዦ ጎሜዝ በ11ኛው ደቂቃ ተቀይሮ ሜዳ ገብቶ ነበር፡፡

ይሁንና ተጨዋቹ ከስድስት ሳምንታት ጉዳት በሁዋላ የመጀመሪያ ጨዋታውን ባደረገበት መርሀግብር ለተጨማሪ ጉዳት መጋለጡን ቢቢሲ ስፖርት ዘገቧል፡፡

በውድድር አመቱ ለክለቡ 10 ጨዋታዎችን ብቻ ያደረገው ተከላካዩ የደረሰበት የጡንቻ መሳሳብ ጉዳት ከባድ መሆኑን አሰልጣኝ አርን ስሎት ተናግረዋል፡፡

ተጨዋቹ የቀዶ ህክምና እንደሚያስፈልገው እየተነገረ ሲሆን የጉዳቱ መጠኑ ለረጅም ጊዜ ከሜዳ ሊያርቀው እንደሚችል አሰልጣኙ አክለዋል፡፡

ወደ አቋሙ ለመመለስ ጠንክሮ ሲሰራ ቆይቷል፤ነገርግን ከጉዳቱ ማገገም አልቻለም ምናልባት በውድድር አመቱ መጨረሻ አገግሞ ሊቀላቀለን ይችላል ነው ያሉት ስሎት፡፡

እ ኤ አ በ2015 ከቻርልተን አትሌቲክ የአንፊልዱን ክለብ የተቀላቀለው ተከላካዩ በቀዮቹ ማልያ 149 ጨዋታዎችን አድርጓል፡፡

በበላይነህ ይልማ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review