የመዲናዋን ገፅታ የቀየሩ እና በዓለም መድረክ ላይ እዉቅና የተገኘባቸዉ ስራዎች መሰራታቸዉን የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሺን ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ እናትዓለም መለሰ ገለጹ

You are currently viewing የመዲናዋን ገፅታ የቀየሩ እና በዓለም መድረክ ላይ እዉቅና የተገኘባቸዉ ስራዎች መሰራታቸዉን የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሺን ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ እናትዓለም መለሰ ገለጹ

AMN – ግንቦት 14/2017 ዓ.ም

በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የሚገኙ የሚዲያ እና የኮሙኒኬሺን ባለሙያዎች “የተደራጀ ኮሙኒኬሽን እና ሚዲያ የሀገራዊ መግባባት ካስማ ፤የትውልድ ግንባታ መሠረት ነው” በሚል መሪ ሀሳብ ዉይይት አድርገዋል::

የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ እናትዓለም መለሰ በቪዲዮ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ባለፉት የለውጥ አመታት የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ እና የከተማዋን ገፅታ የቀየሩ ለዓለም ሃገራትም የሚታዩ እና ዘመን ተሻጋሪ ስራዎች መሰራታቸዉን ተናግረዋል ::

በከተማዋ የዜጎችን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ግዙፍ ፕሮጅክቶች ተገንብተዋል ያሉት ኃላፊዋ፣ ስራዎቹም በዓለም መድረክ ላይ እዉቅና የተገኘባቸዉ እና ለሌሎች ሃገራት ጭምር ተሞክሮ መሆን ችለዋል ብለዋል::

የሚዲያ ባለሙያዎች የተሰሩ ስራዎችን በማስተዋወቅ ታሪካዊ እና የዜግነት ኃላፊነታቸዉን መወጣት እንደሚገባቸውም አሳስበዋል::

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር አዲሱ ሻንቆ በበኩላቸው፣የሚዲያ ባለሙያዎች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ስራ በመስራት ዜጎችን የጋራ የሚያደርጉ እሴቶችን ማጎልበት ይገባል ብለዋል::

በቴዎድሮስ ይሳ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review