ባለሙያዎቹ በቦሌ ክፍለ ከተማ ተጀምረው በአጭር ጊዜ የተጠናቀቁና እየተጠናቀቁ የሚገኙ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው።
በክፍለ ከተማው በመጀመሪያው ዙር የለሙ የኮሪደር ቦታዎች፣ በሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት እየለሙ ያሉ ልማቶች፣ የቦሌ ቡልቡላ ፓርክ፣ በወረዳ 7 በአጭር ጊዜ ተጀምሮ ወደመጠናቀቅ ምዕራፍ የደረሰ ደረጃውን የጠበቀ ጤና ጣቢያ፣ የወጣት ሰብዕና መገቢያ፣ የማስፋፊያ የተደረገባቸው የትምህርት ተቋማትና ሌሎችም የጉብኝቱ አካል ናቸው።
በጉብኝት የክፍለ ከተማው የስራ ሀላፊዎች፣ የሚዲና የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎችን ጨምሮ ታዋቂ አርቲስቶች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ከጉብኝቱ በኋላ ውይይት እንደሚካሄድ ተመላክቷል።
በሄለን ጀምበሬ