የስንዴ መኸርን የመሰብሰብ ሒደት በመጀመሩ ከአጨዳ እስከ ጎተራ የሁሉም እገዛ ያስፈልጋል፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

AMN- ህዳር 9/2017 ዓ.ም

የስንዴ መኸርን የመሰብሰብ ሒደት በመጀመሩ ከአጨዳ እስከ ጎተራ የሁሉም እገዛ ያስፈልጋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አሳሰቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት የስንዴ መከር ተጀምሯል ብለዋል።

እናም በዚህ ዓመት ብዙ ምርት ስላለን ይህን ሂደት በሀገር አቀፍ ደረጃ በትብብር ማፋጠን አለብን ሲሉ ገልጸዋል ።

ከአጨዳ እስከ ጎተራ የሁላችንንም ትግግዝ ይፈልጋል ሲሉም አመልክተዋል ።

በተጨማሪም ለመጪው የበጋ የስንዴ ምርት መዘጋጀት አለብን ብለዋል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review