ስኬት ባንክ ከሚሰጣቸው የባንክ አገልግሎቶች በተጨማሪ የተለያዩ ማህበራዊ ኃላፊነቶች ላይ የድርሻውን በወጣት ላይ ይገኛል፡፡
የባንኩ አመራሮችና ሰራተኞችም በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከበረውን የዓለም አቀፍ ደም ለጋሾች ቀን ምክንያት በማድረግ ከኢትዮጵያ ደምና ሕብረ ህዋስ ባንክ ጋር በመተባበር “ደም እንለግስ ህይወት እናትርፍ!” በሚል መሪ ሀሳብ ትናንት በዋና መ/ቤት የደም ልገሳ መርሃ ግብር አካሄደዋል፡፡

አመራርና ሰራተኞቹ በሰዉ ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት የደም እጥረት ገጥሟቸው ለሚጠባበቁ ህሙማን ለመድረስ እና ህይወታቸውን ለማዳን የሚያደርጉትን ርብርብ አጠናክረዉ የሚቀጥሉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡